ባዬ (Combretum paniculatum) ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ ተክል ነው።
በረጀም ዛፎች ላይ የሚያድግ ቊጥቋጥ ነው። ደማቅ ቀይ አበቦች አሉት።
ሌላ ዝርያ Terminalia schimperiana ደግሞ «ባዬ» ተብሏል፤ ይህም መለየት ይፈልጋል።
በሙቅ፣ እርጥብ ሥፍራዎች በወለጋና ጅማ ይታያል።
ትኩስ አበቦቹ ተደቅቀው ጭማቂው ለዓይን በሽታ ለማከም ይጠቀማል። ይህ ተክል ወይም ምናልባት Terminalia schimperiana ደግሞ ቁምጥናን ለማከም ተጠቅሟል።[1]